አንድነት 14ኛ ዓመት ቁ. 22 ዓርብ ታህሳስ 23 ቀን 2002 ዓ.ም
አሁን በሥልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ መንግሥት ሥልጣን ከጨበጠበት ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ አገሪቱን ለራሱ በሚያመቸው መንገድ በዘርና በቋንቋ ከፋፍሎ ለአለፉት 18 ዓመት ሲገዛ ቆይቷል፤ ይህን በመከፋፈል ላይ የተመሠረተ አስተዳድር የሚቃወሙትን ዜጎች በመወንጀል፣ በማሳደድና አገር ጥለው እንዲሰደዱ ከፍተኛ ጫና አድርጓል:
ኢህአዴግ ሥልጣን ከያዘበት ቀን ጀምሮ ከራሱ ሰዎች በስተቀር ለአንተ አንድም ቀን እድል ገጥሞህና በምታደርገው እርምጃ ሁሉ ቀንቶህ አያውቅም፤ ይህ በመሆኑም ድሮ የነበረህን የውስጥ ደስታና የእርስ በእርስ ፍቅር አጥተህ በዘርና በጎሳ በመለያየት በመናቆር ላይ ነህ፣ ሰው ሰራሽ በሆነው የኑሮ ውድነትም በመጠበስ ላይ ትገኛለህ፡፡
የአገሪቱ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ፍትህ የጎደለው ከመሆኑ የተነሳ ጥቂት አፍቃሬ ኢህአዴግ የሆኑ ግለሰቦችን በአንድ ጀምበር ሚሊየነር ሲያደርግ ብዙ ዜጎችን ደግሞ ወደ ድህነት አዘቅት ውስጥ ይወረውራቸዋል የኢህአዴግ መንግሥት በየጊዜው የሚያወጣቸው ብሔራዊም ሆነ ክልላዊ ፖሊሲዎቹ ለሀገርም ሆነ ለሕዝብ ጥቅም ታስቦ ሳይሆን ለገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ትርፍ እንዴት እንደሚያስገኝ በታሳቢነት ተይዞ አይደለምን? ልጆችህ በአገራቸው ላይ ሥራ በማጣታቸው የተነሳ ወደ ተለያዩ የአረብ አገራት ለባርነት በመሰደድ ላይ ባሉበት በአሁኑ ወቅት የኢህአዴግ መንግሥት አናጺና ግንበኛ ከፓኪስታን፣ የእንጨትና የብረት ሰራተኛ ከቱርክና ከቻይና በማምጣት የኢኮኖሚ ወረራ እንዲደርስብህ አድርጓል:: በዓለም ላይ ለአገርና ለሕዝብ የሚቆረቆር መንግሥት ያላቸው አገሮች የሚያደርጉት ሥራውን የሚያከናውን ዜጋ በአገሪቱ እስካልጠፋ ድረስ ኮንትራክተሮችም ሆነ የእርዳታ ድርጅቶች ሠራተኛ ከውጭ ማምጣት አይችሉም አይፈቀድላቸውምም፤ ይሁን እንጂ የእኛ መንግሥት በሥልጣን ላይ የሚያቆየውን የፖለቲካ ትርፍ በማሰብም ሆነ በሌላ ስውር ምክንያት ከእንደዚህ ያለ የኢኮኖሚ ብዝበዛ ጥቃት ሊጠብቀን አልቻለም ፈቃደኛም ሆኖ አልተገኘም::
ለማንበብ ከዚህ ላይ ይጫኑ