About Us
  • About Kinijit AEUP
  • Political Program
  • Election 2005
  • Election 2010
  • USA
  • Canada
  • Europe
  •   News
  • Amharic
  • English
  • Washington Update
  •   Editorial & Opinions
  • Editorial
  • Opinion
  •   Media
  • Audio
  • Video
  •   Press Release
  • English
  • Amharic
  •   Burning Issues
  • Economy
  • Education
  • Health
  • HR2003 to S3457
  • Regional Crisis
  • Politics & Democracy
  • Others
  •   Facts about Ethiopia
  • All Ethiopia Gallery
  •   Take Action
  • Make a Contribution
  • Join our Supporters
  •    Subscribe to Andenet
         Gazette
      Calendar
  • Calendar
  •  
     
      Home Contact Us   Font help

    68ኛው የድልና የነጻነት በዓል ተከበረ


    “ወጣቱ ዲሞክራሲን የመገንባት ኃላፊነት አለበት”
    መኢአድ

    ሚያዝያ 27 ቀን 2ዐዐ1 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከአምስት ዓመታት የጣሊያን ወረራ ነጻ የወጣችበትንና አርበኞች በድል ወደ አዲስ አበባ የገቡበትን 68ኛውን የድልና የነጻነት በዓል በአራት ኪሎ የድል ሐውልት አርበኞችና ሌሎችም ኢትዮጵያውያን በተገኙበት የመላው የኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ ምክትል ፕሬዝዳንትና የምስራቅ ኢትዮጵያ ቀጣና ኃላፊ ሻለቃ ጌታቸው መንግስቴ የድል በዓሉን በተመለከተ ለአንድነት ጋዜጣ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ሕዝብ የአርበኝነት ተጋድሎውን በላቀ መንፈስ የገለጠበትና አንድነቱን ያሳየበት ነው ብለዋል፡፡ ሕዝቡ ለነጻነቱ ሲል በጣሊያን ወራሪ ኃይል ፕሮፖጋንዳና ዘመናዊ የጦር መሳሪያ ሳይበገር ጾታና እድሜ ሳይለይ በአርበኝነት የታገለበትና ድል የተቀናጀበት ዕለት መሆኑንም ጨምረው ገልፀዋል፡፡
     
    ሚያዝያ 27 የድል በዓል ሲከበር እስካሁን በሕይወት ለመቆየት የቻሉት ጥቂት አባትና እናት አርበኞች ከነ ትጥቃቸው በወኔ የነበረውን ትግል እንዴት እነደነበር ሲገልፁ ማየት ለአዲሱ ኢትዮጵያዊ ትውልድ የሚያኮራ ነው ያሉት ሻለቃ ጌታቸው መንግስቴ የአሁኑ ትውልድ ከነዚህ ቀደምት አርበኞች የነጻነት ዋጋንና የሐገር ፍቅርን ብዙ ሊማሩት የሚገባ ቁም ነገር አለ በማለት አስረድተዋል፡፡
     
    የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዛኛው ታሪኩን ያሳለፈው ከውጭ ከመጡ ወራሪ ኃይሎችና ከራሱ አምባገነን መሪዎች ጋር እልህ አስጨራሽ በሆነ ትግል ሲሆን ለዲሞክራሲ ልዕልና የሚያደርገው አሁንም ትግል ዛሬም መፍትሄ አላገኘም፡፡ በመሆኑም ዛሬ ከወራሪ የውጭ ጠላት ነጻ  የሆንበትን የድል በዓል ሲያከብር ለዲሞክራሲ ልዕልናና ለመልካም አስተዳደር መመስረት ዛሬም እየታገለ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ከዛሬ 68 ዓመት በፊት ጀግኖች አርበኞች የፋሺስት ወራሪ ኃይልን ድል ያደረጉበትን ቀን ስናከብር የአሁኑ ትውልድን በሰላማዊ መንገድ በመታገል ነጻና ዲሞክራሲ የሰፈነባት ኢትዮጵያን እንደሚገነባ ምክትል ፕሬዝዳንቱ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡
    መኢአድ እየተከተለ ባለው የሰላማዊ የትግል ስልት የፓርቲው አመራር፣ አባላትና ደጋፊዎች የሕይወት፣ የአካልና የንብረት መስዋእትነትን መክፈላቸውን ጠቁመው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነጻነትና መብት ተከብሮ እስኪረጋገጥ ድረስ መኢአድ ከሕዝቡ ጋር በሰላማዊ መንገድ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ሻለቃ ጌታቸው አብራርተዋል፡፡
     
    አርበኝነት ጠብመንጃ በመያዝ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ውጤታማ የሆነ ሁሉ የሐገሪቱ ጀግና መሆኑን የገለፁት ሻለቃ ጌታቸው ወጣቱ ትውልድ ሐገሩን በልማት በመገንባትና በሰላማዊ መንገድ በመታገል ነጻነቱን የማስከበር ኃላፊነት አለበት ብለዋል፡፡
     
    የመኢአድ ምክትል ፕሬዘዳንት እንዳሉት የድል በዓሉን ስናከብር በአያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ አዕምሮ የሚታወሰው አገራችን በኢኰኖሚ ራሷን ችላ ለዜጐቿ የተመተቸና በታሪኳ ብቻ ሳይሆን በዕድገት የሚመኩባት አገር ለመሆን የሚያስችላትን ስርአትና አስተዳደር ለመመስረት ዛሬም በእልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ እንደምትገኝ ተገንዝቦ ለትግሉ ሁሉም የዜግነቱን አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚጠበቅበት አብራርተዋል፡፡
     
    ጠላትን በተባበረ ክንዱ ድል ማድረግ ልማዱ የሆነው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ዛሬም በድህነትና በኋላቀርነት ላይ የጋራ ክንዱን ማንሳት እንዳለበት ገልፀው የዓለምን የዴሞክራሲ ስርዓት ለራሳቸው ጥቅም በሚመች መልኩ አዛብተው የሚተረጉሙትን አካላት በሰላማዊ መንገድ ሊቃወሟቸው እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
     
    የድልና የነጻነት በዓል ለአምስት ዓመታት በዱር በገደል ሲዋጉ የነበሩት የኢትዮጵያ አርበኞች በብዙ መስዋእትነት የራሳቸውንና የሐገራቸውን ነጻነት አስከብረው አዲስ አበባ የገቡበት የመታሰቢያ ቀን ነው፡፡

    Comments



       Type in your comments for this article
    Name (appears on your post)
    Email
    Comment

    Write the characters in the image above

    Search News:
    In all newsIn News Amharic

    Advanced Search
    Archive:
    Published in:
    Published between
    and
    Categories:
    all categories
    one or more of the following categories (select as many as you want)
    History
    World News
    Opinion
    Editorial
    News English
    Washington Update
    News Amharic
    Media Audio
    Media Video
    Kinijit AEUP Radio
    Africa News


    Most Viewed News Amharic
    የፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ዕረፍት አሥረኛ ዓመት ግንቦት 6 ይታሰባል
    በምስራቅ ጐጃም አንድ ተማሪ በታጣቂዎች ተገደለ
    በሰሜን ጐንደር የእስረኞች አያያዝ አሳሳቢ መሆኑ ተገለፀ
    መኢአድ “ሊበራል ኦፕን-ኤየር ኮሌጅ” መክፈቱን አስታወቀ
    መንግስት ጐንደር ውስጥ ከ6ዐ በላይ ሰዎችን ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ለአርባ ቀን ያሕል አስሮ መልቀቁ ተገለፀ፡፡
    የጐፋ ልዩ ዞን የገዢው ፓርቲ የጽ/ቤቶቹን ባንዲራ እያወረደበት መሆኑን መኢአድ ገለፀ
    የመኢአድ የደጀን ወረዳ ልዩ ዞን የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አካሄድ
    የመኢአድ የአርባ ምንጭ ዞን ሰብሳቢና ፀሐፊ ያለ ሕግ አግባብ ታሰሩ
    የመኢአድ የኪነት ቡድን ሞረሽ በበዓሉ ላይ ጣዕመ ዜማዎች በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡
    የመኢአድ የአ.አ ወጣቶች በበዓሉ ላይ ንግግር አደረጉ፡፡