About Us
  • About Kinijit AEUP
  • Political Program
  • Election 2005
  • Election 2010
  • USA
  • Canada
  • Europe
  •   News
  • Amharic
  • English
  • Washington Update
  •   Editorial & Opinions
  • Editorial
  • Opinion
  •   Media
  • Audio
  • Video
  •   Press Release
  • English
  • Amharic
  •   Burning Issues
  • Economy
  • Education
  • Health
  • HR2003 to S3457
  • Regional Crisis
  • Politics & Democracy
  • Others
  •   Facts about Ethiopia
  • All Ethiopia Gallery
  •   Take Action
  • Make a Contribution
  • Join our Supporters
  •    Subscribe to Andenet
         Gazette
      Calendar
  • Calendar
  •  
     
      Home Contact Us   Font help

    መኢአድ አበረታች ሥራ መስራቱ ተገለፀ


    የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ በመላው የሐገሪቱ ክፍሎች 63 ጽ/ቤቶችን መክፈቱን የፓርቲው ሕዝብ ግንኙት ኮሚቴ ኃላፊ ወ/ሪት መሶበወርቅ ቅጣው ለአንድነት ጋዜጣ ገለፁ፡፡

    ከቅንጅት አመራሮች መፈታት በኋላ የተወሰኑ የአመራር አባላት እራሳቸውን ከቅንጅት ፓርቲ ቢያገሉም በኢንጂነር ኃይሉ ሻውል የሚመራው ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ከአባላትና ደጋፊዎች ጋር በመሆን ፓርቲውን የማጠናከር ሥራ በማከናወን ላይ መሆናቸውን ኃላፊዋ ጠቅሰዋል፡፡
     
    ቅንጅት ጠቅላላ ጉባኤውን ሰኔ 2 2000 ዓ.ም ካካሄደና ስያሜውንም ነሐሴ 2 2000 ዓ.ም ወደ መኢአድ ከቀየረ በኋላ ፓርቲው ይበልጥ ተጠናክሮ በሰሜን ፣ በምስራቅ በምእራብና በደቡብ ኢትዮጵያ ቀጣናዎች 28 የዞንና 35 የወረዳ ጽ/ቤቶች እንደተከፈተ ተገልፀዋል፡፡
     
    የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዋ በሀገሪቱ ባሉ ክልሎች የፓርቲውን የጽ/ቤቶች ብዛትን በመተንተን ሲያስረዱም በደቡብ ኢትዮጵያ 32፣ በሰሜን ኢትዮጵያ 20፣ በምስራቅ ኢትዮጵያ 5፣ በምእራብ ኢትዮጵያ 4፣ የዞንና የወረዳ ጽ/ቤቶች እንዲሁም በአዲስ አበባ 2 ጽ/ቤቶች እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡
     
    አብዛኛዎቹ የወረዳ ጽ/ቤቶች ሕዝቡ ለፓርቲው ካለው ፍቅርና ድጋፍ እንዲሁም ለሰላማዊ ትግል ባለው ቀናና ቁርጠኛ አመለካከት ፓርቲው ከሚያደርገው ድጋፍ ውጭ አባላት በራሳቸው ተነሳሽነት በግላቸው የጽ/ቤቶችን ኪራይና ሌሎች ወጪዎችን በመሸፈን የፓርቲውን ሥራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡
     
    በአሁኑ ወቅት ከተለያዩ የሐገሪቱ ክፍሎች ፓርቲው ጽ/ቤቶችን እንዲከፍት ጥሪ እያደረጉ የሚገኙ ዞኖችና ወረዳዎች ብዙ ናቸው ያሉት ወ/ሪት መሶበወርቅ መኢአድ ወደፊት ጥያቄ ባቀረቡ ዞኖችና ወረዳዎች ላይ ጥናት በማድረግ ጽ/ቤቶችን ለመክፈት መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡
     
    የቅንጅት አመራር አባላት እስር ቤት ሲወጡ በመላው ሀገሪቱ የነበሩት ጽ/ቤቶች በገዥው ፓርቲ ተዘግተው የነበረ ሲሆን የቀሩትም ከአምስት የማይበልጡ እንደነበሩና መኢአድ ግን ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ብቻ የጽ/ቤቶቹን ቁጥሮች ወደ 63 ማሳደግ መቻሉ ፓርቲው በሕዝብ ዘንድ ያለውን ድጋፍና ተቀባይነት በግልጽ የሚያሳይ ነው ሲሉ የሕዝብ ግንኙት ኃላፊዋ ወ/ሪት መሶበወርቅ ቅጣው ገልፀዋል፡፡

    Comments



       Type in your comments for this article
    Name (appears on your post)
    Email
    Comment

    Write the characters in the image above

    Search News:
    In all newsIn News Amharic

    Advanced Search
    Archive:
    Published in:
    Published between
    and
    Categories:
    all categories
    one or more of the following categories (select as many as you want)
    History
    World News
    Opinion
    Editorial
    News English
    Washington Update
    News Amharic
    Media Audio
    Media Video
    Kinijit AEUP Radio
    Africa News


    Most Viewed News Amharic
    መኢአድ በክልል ለሚገኙ የዞን የሥራ ኃላፊዎች ስምምነት በተደረሰበት ሰነድ ላይ ማብራሪያ ሰጠ
    በምስራቅ ጐጃም አንድ ተማሪ በታጣቂዎች ተገደለ
    በሰሜን ሸዋ ዞን ገዥውን ፓርቲ በመቃወማቸው ለስደት መዳረጋቸውን ገለፁ
    68ኛው የድልና የነጻነት በዓል ተከበረ
    መኢአድ በሰሜን ጐንደርና በትግራይ ተጨማሪ ጽ/ቤቶችን ከፈተ
    መኢአድ በባሕርዳር ከተማ ታለቅ ስብሰባ አካሄደ - የመጀመሪያዉን የምርጫ ደወል አሰማ
    በሰሜን ጐንደር የእስረኞች አያያዝ አሳሳቢ መሆኑ ተገለፀ
    መኢአድ “ሊበራል ኦፕን-ኤየር ኮሌጅ” መክፈቱን አስታወቀ
    መንግስት ጐንደር ውስጥ ከ6ዐ በላይ ሰዎችን ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ለአርባ ቀን ያሕል አስሮ መልቀቁ ተገለፀ፡፡
    የጐፋ ልዩ ዞን የገዢው ፓርቲ የጽ/ቤቶቹን ባንዲራ እያወረደበት መሆኑን መኢአድ ገለፀ