About Us
  • About Kinijit AEUP
  • Political Program
  • Election 2005
  • Election 2010
  • USA
  • Canada
  • Europe
  •   News
  • Amharic
  • English
  • Washington Update
  •   Editorial & Opinions
  • Editorial
  • Opinion
  •   Media
  • Audio
  • Video
  •   Press Release
  • English
  • Amharic
  •   Burning Issues
  • Economy
  • Education
  • Health
  • HR2003 to S3457
  • Regional Crisis
  • Politics & Democracy
  • Others
  •   Facts about Ethiopia
  • All Ethiopia Gallery
  •   Take Action
  • Make a Contribution
  • Join our Supporters
  •    Subscribe to Andenet
         Gazette
      Calendar
  • Calendar
  •  
     
      Home Contact Us   Font help

    መንግስት ጐንደር ውስጥ ከ6ዐ በላይ ሰዎችን ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ለአርባ ቀን ያሕል አስሮ መልቀቁ ተገለፀ፡፡


     

    መንግስት ጐንደር ውስጥ ከ6ዐ በላይ ሰዎችን ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ለአርባ ቀን ያሕል አስሮ መልቀቁ ተገለፀ፡፡
     
            የ2001 ዓ.ም የጥምቀት በዓል መከበርን ተከትሎ የገዥው ፓርቲ በኦርቶዶክስና በእስልምና ሐይማኖቶች መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ተጠያቂ በማድረግ 6ዐ በላይ ሰዎች ያለፍረድ ቤት ትእዛዝ ለአርባ ቀናት ያህል አስሯቸው እንደነበር ተገለፀ፡፡
     
    አቶ ያሬድ ግርማ የመኢአድ ማዕከላዊ ምክር ቤት አባልና የሰሜን ጐንደር ሰብሳቢ በዞኑ ውስጥ ባላቸው ከፍተኛ ተደማጭነት ምክንያት ከሥልሳዎቹ ጋር በተመሳሳይ ውንጅላ ታስረው እንደነበረ  አቶ ጌታነህ ዓለም የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት አባልና የሰሜን ኢትዮጵያ ቀጠና አደራጅ ገልጸዋል፡፡
     
    እንደ አቶ ጌታነህ ገለጻ ታሳሪዎቹ በሃይማኖት ሰበብ ይያዙ እንጂ በዚህ አጋጣሚም የተቃዋሚ ፓርቲ አባለባትም እንዲታሰሩ ተደርገዋል፤ ለምሳሌ አቶ ያሬድ ግርማ በግጭቱ ወቅት በቦታው ያልነበሩና በሰላም ወዳድነታቸውም በአከባቢው የታወቁ እንደነበሩ አስታውቀው መንግስት ጠንካራ የመኢአድ አባል በመሆናቸው ብቻ እረብሻውን አሳቦ አብሮ በማሰር አርባ ቀን እንዳጉላላቸው ጠቅሰዋል፡፡
     
          ይህ የመንግስት እርምጃ ፍጹም የሆነ የሰብአዊ መብት ጥሰት እንደሆነ ከሚያሳዩ ነገሮች መካከል፡-
    • ይህን ያህል ሰው የታሰረው ከፍርድ ቤት ትእዛዝ ውጭ ህገወጥ በሆነ መንገድ መሆኑ፣ ታሳሪዎቹ ድርጊቱ በተፈፀመበት የጥምቀት ቦታ አለመኖራቸውና ከየቤታቸው መለቀማቸው፣ ለአርባ ቀናት ሲታሰሩ ምንም ዓይነት መረጃና ክስ ሳይቀርብባቸው መሆኑና ወንጀል እንዳልፈፀሙ እየታወቀ አቃቤ ሕግ ጉዳዩ ከዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በላይ ነው በማለት ወደ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይዛወር ብሎ  ለፍርድ ቤቱ ሐሳብ ማቅረቡና ካለ ሶስት ሺ ብር ዋስ አትለቀቁም በማለት ሰላማዊዎቹን ሰዎች ማስጨነቅ የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡  
    ይህ የሚያሳየው በአሁኑ ወቅት ያለው የሕግ አሰፈፃሚ አካል አሠራር ለኢህአዴግ እና ለኢህአዴጋውያን ብቻ እንጂ ለሌሎች ዜጐች ያልቆመ መሆኑን ያረጋገጠ ነው ብለዋል፡፡

    Comments



       Type in your comments for this article
    Name (appears on your post)
    Email
    Comment

    Write the characters in the image above

    Search News:
    In all newsIn News Amharic

    Advanced Search
    Archive:
    Published in:
    Published between
    and
    Categories:
    all categories
    one or more of the following categories (select as many as you want)
    History
    World News
    Opinion
    Editorial
    News English
    Washington Update
    News Amharic
    Media Audio
    Media Video
    Kinijit AEUP Radio
    Africa News


    Most Viewed News Amharic
    በምስራቅ ጐጃም አንድ ተማሪ በታጣቂዎች ተገደለ
    በሰሜን ሸዋ ዞን ገዥውን ፓርቲ በመቃወማቸው ለስደት መዳረጋቸውን ገለፁ
    68ኛው የድልና የነጻነት በዓል ተከበረ
    መኢአድ በባሕርዳር ከተማ ታለቅ ስብሰባ አካሄደ - የመጀመሪያዉን የምርጫ ደወል አሰማ
    በሰሜን ጐንደር የእስረኞች አያያዝ አሳሳቢ መሆኑ ተገለፀ
    መኢአድ “ሊበራል ኦፕን-ኤየር ኮሌጅ” መክፈቱን አስታወቀ
    መንግስት ጐንደር ውስጥ ከ6ዐ በላይ ሰዎችን ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ለአርባ ቀን ያሕል አስሮ መልቀቁ ተገለፀ፡፡
    የጐፋ ልዩ ዞን የገዢው ፓርቲ የጽ/ቤቶቹን ባንዲራ እያወረደበት መሆኑን መኢአድ ገለፀ
    የመኢአድ የደጀን ወረዳ ልዩ ዞን የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አካሄድ
    የመኢአድ የአርባ ምንጭ ዞን ሰብሳቢና ፀሐፊ ያለ ሕግ አግባብ ታሰሩ